Sunday, 3 November 2013

 ምንፍቅና ይቅርታ ይመልሰው ይሆን?......ሰሞንኛ 
“የበደልናትን ቤ/ክርስቲያን እንክሳለን፤ ይዘን የወጣነውን ህዝብ መልሰን እናመጣለን፤ ላጠፋነው ጥፋትም ቤ/ክር ይቅርታ ታድርግልን፡፡ ”ተሀድሶያውያን፡፡……ጉዳያቸው በቅዱስ ሲኖዶስ ተይዞ በመታየት ላይ የሚገኘው የበጋሻው ደሳለኝ እና የያሬድ አደመን ጉዳይ በእርቅ መንገድ መፍትሄ እንዲፈለግለት በመንቀሳቀስ ላይ የምትገኘው ዘማሪት ፋንቱ ወልደ መሆኗ ታውቋል፡፡በጋሻውና ያሬድ አደመ ከላይ የተገለፀውን የተናገሩት ዘማሪት ፋንቱ ሁለቱንም ወደ “ብፅዕ አቡነ ገብርኤል” የሲዳማ፤ጌዲዮ፤አማሮ፤ቡርጂ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ዘንድ እንደወሰደቻቸው ሲሆን እነበጋሻውም የአባታችን እግር ላይ በመውድቅ ይቅርታ ጠይቀዋል፡፡ብፅዕነታቸውም “እኔን የሰደባችሁኝን በግሌ ይቅርታ ብያችኃለው የቤ/ክርስቲያንን ግን ጉዳዩ በቅዱስ ሲኖዶሱ እየታየ ስለሆነ ውሳኔውን ከውደ በላይ ጠብቁ” በማለት መልስ ሰተዋል፡፡ዘማሪት ፋንቱ ማስታረቋን በመቀጠል እነበጋሻውን ወደ “ብፅዕ አቡነ ሉቃስ” የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊ ያቀረበች ሲሆን ብፅዕ አባታችንም “ሰው ይቅርታ ሲጠይቅ እንቢ አይባልም ይቅርታን መግፋት ተገቢ አይደለም ሆኖም ጉዳያችሁ አስቀድሞ በሲኖዶሱ የተያዘ በመሆኑ ትክክለኛውን ምላሽ ከዚያ ታገኛላችሁ” ብለዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ እነ በጋሻው ከሚቃረኗቸው ሰባኪያንና ዘማሪያን ጋር ቀርበው ለመነጋገርም ተስማምተዋል ህዝቡንም ቤ/ክርም ይቅርታ እንጠይቃለን ብለዋል፡፡ይሁን እንጂ እንደ እኔ ከሆነ ቤ/ክርስቲያን ልትጠነቀቅባቸው የሚገቡ ጉዳዮችም አሉ ከይቅርታው ጋር ተያይዞ፡፡ ይህ ጉዳይ የመታረቅ እና ያለመታረቅ ጉዳይ አይደለም፡፡እነዚህ ሰዎች ከማንም በላይ ቤ/ክርንን አዋርደዋል፡፡ትምህርቷን በማጣመም በመበረዝ በክህደት ጎዳና ባለማወቅም ሆነ በማወቅ የነጎዱ ነበሩ፡፡ ብለው ብለው የጀመሩት ጎዳና የት እንደሚያደርሳቸው ሲያውቁ በይቅርታ ካባ መምጣታቸው ተገቢ አይደለም፡፡ ከልብ ተፀፅተው ከሆነም በቪሲዲያቸው፤በመፅሐፍቶቻቸውና በብሎጎቻቸው በመዝሙሮቻቸው ያስተላለፏቸው ኑፋኬዎች በሊቃውንት ጉባኤ ታይቶ፤ስራቸው ተመዝኖ ቅዱስ ሲኖዶስ መክሮበት ከሚሰጠው ውሳኔ በኃላ ይቅርታው መሆን አለበት፡፡ሌላው ይቅርና ግራና ቀኛቸውን ያልተመለከቱ ምዕመናንን በመያዝ ድንግል ማርያምን እና ቅዱሳንን ሲሰድቡ ለነበሩበት ሁኔታ እንኳን መልስ

No comments:

Post a Comment